
C.O.Dr.Ambachew Woreta Foundation ForTadewos Tantu
Donation protected
የ80 ዓመቱ ጋዜጠኛ፣ ደራሲና መምህር አቶ ታዴዎስ ታንቱ ከአምባገነኖች ጋር ፊት ለፊት በመጋፈጥ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ በሐቀኝነት ሲታገሉ በተደጋጋሚ ጊዜ በሕወሓትና በኦሮሙማ መራሹ መንግሥት መታሰራቸውና አሁንም በድጋሚ በእስር ላይ መሆናቸው ይታወቃል። በዚህም ምክንያት ከዚህ በፊት አንዲት ግለሰብ ሳራ ተስፋዬ በሚል ስም በጎፈንድሚ ገንዘብ ከሰበሰበች በኋላ ገንዘቡን ለአቶ ታዴዎስ ወይም ለቤተሰባቸው ባለመድረሷ ገንዘቡ እንዳይወጣ ታግዷል። ቀጣዩ ሂደትም በሕግ አግባብ ተይዞ ይገኛል። (የETHIO 360ን August 19 ና 20ና 28, 2020 ፕሮግራም ይመልከቱ) የሕግ ሂደቱ ጊዜ ስለሚወስድና ጋሼ ታዴዎስና ቤተሰባቸው ደግሞ ከባለፈው እስራታቸው በከፋ እስርቤት ውስጥና ችግር ላይ ስለሚገኙ ቀደም ሲል በግለሰቧ ጎፈንድሚ በኩል የለገሳችሁ ሰዎች ገንዘባችሁን በማስመለስ ወደ እዚህና አቶ ታዴዎስ ታንቱ በአበበ በለው ቀጥታ ስርጭት ላይ በተናገሩትና እውቅና በሰጡበት (Read more የሚለውን ከተጫኑ በኋላ ቪዲዮውን ይመልከቱ) በዶ/ር አምባቸው ወሮታ ፋውንዴሽን በኩል ወደ ተከፈተው ጎፈድሚ ማስተላለፍ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ቀደም ሲል ጋሼ ታዴዎስን በማገዝ ያልተሳተፋችሁ ሀገርና ወገን ወዳጆች በሙሉ ለእኚህ የ80 ዓመት አዛውንት፣ ለእውነት አባትና ለቤተሰባቸው እገዛ ታደርጉ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ጋሼ ታዴዎስ ታንቱን ለመርዳት የተቋቋመ ጊዜያዊ ኮሚቴ።
ጋሼ ታዴዎስ ታንቱን ለመርዳት የተቋቋመ ጊዜያዊ ኮሚቴ።
Organizer and beneficiary
Dr.Ambachew Woreta
Organizer
Baltimore, MD
DR.Ambachew Woreta
Beneficiary