Main fundraiser photo

Church Construction Fund

Donation protected
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች ምዕመናን እና ምዕመናት:-

ፅርሃ አርያም ቅድስት ስላሴ ቤተከርስትያን ከሐዋርያትና ከአበው ሲወርድ ሲወራረድ በመጣው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ስርዓት መሰረት ጥንታዊ እምነታችን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በእግዚአብሔር ፈቃድ በአውስትራሊያ ሃገር ሕግ መሰረትና በምእመናን የበላይነት መርህ የተቋቋመች ናት።  

በዚሁ መሰረት ቤተ ክርስቲያኗ ከመደበኛ የእሑድ ጠዋት የቅዳሴ አገልግሎት በተጨማሪ የስብከተ ወንጌል፡ የጸሎተ ፍታት፡ የክርስትና፡የተክሊል ጋብቻ አገልግሎት እና ለወጣቶች የሰንበት ት/ቤት አገልግሎት በመስጠት ላይ ትገኛለች። ቤተ ክርስቲያኗ በአሁኑ ሰዓት ከላይ የተዘረዘሩትን አገልግሎት የምታቀርበው በኪራይ ቤት ውስጥ በመሆኑ የታሰበውን ያህል በአስተማማኝነት ለመቀጠል እና ለማስፋፋት አልቻለችም።

እግዚአብሔር ፈቅዶ በአርመዳይል ከተማ አስተዳደር (14 Mackenzie Grove,Kelmscot WA 6111) ወደ 2.1 ሄክታር የሚሸፍን መሬት ገዝተን የግንባታ ስራ ለመጀመር ብዝግጅት እንገኛለን። “ድር ቢያብር አንበሳ ያስር” ነውና ከልዑል እግዚአብሔር ርዳታ ጋር ምእመናን ከተባበርን ለመግዛትና የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ንብረት ለማድረግ እንደማያዳግት እንተማመናለን። በከተማ አስተዳደሩ ህግ መሰረት ህንፃ ቤተክርስትያኑን ገንብተን ወደ ቦታው ለመግባት ያለን ጊዜ ከ6 ወራት የበለጠ አይደለም። በመሆኑም በየትኛውም የዓለማችን ክፍል የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያንና የቤተ ክርስቲያን ወዳጆች በሙሉ ገንዘብ በመለገስ የበኩላችሁችሁን አስተዋጽኦ እንድታበረክቱልን የበረከትና የታሪክ ተሳታፊዎችም ትሆኑ ዘንድ መንፈሳዊ ጥሪያችንንና ልመናችንን በእግዚአብሔር ስም እናቀርባለን።

ይህን መልእክት ለሚያውቁት ሁሉ በማስተላለፍ በረከቱን ለሁሉም አዳርሱ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
መልአከ ገነት ቀሲስ መሃሪ ወልደኪዳን ተድላ
የደብሩ አስተዳዳሪ

Dear brothers and sisters;
We are the Tsirha Ariyam Kidist Selassie  Ethiopian Orthodox Church here in Perth, Western Australia.

The work and ministry of our church include sanctifying the faithful through God's grace in worship, conducting Divine Liturgy, offering the Sacraments of our Lord Jesus Christ, and enhancing the spiritual life of its followers. These services are in manners consistent with the faith, values and traditions of the Ethiopian Orthodox Tewahedo church.

The faithful have purchased land at 14 Mackenzie Grove Kelmscott, WA 6111), however, due to limited financial resources, and this small community is fervently engaged in fundraising activities to build the church facilities.

You don't have to be part of this church or believe in this particular religion to donate. You can just do it for the common good. This church means a lot to any Ethiopian Orthodox follower especially here in Perth because this is where we get a sense of our culture, tradition and a sense of our community while being away from our country. We are trying to pass on our religious traditions, and the Ethiopian culture to the younger generation and a new church building was needed to do that. 

Any level of assistance you may offer is much appreciated; it is all in the service of our Lord Jesus Christ.
We are grateful for your continued prayers and financial support!

God Bless
Priest Mehari Weldekidan Tedla
Administrator
Donate

Donations 

  • Tesfu Gebrehiwot
    • $100
    • 4 yrs
Donate

Organizer and beneficiary

Perth Kidist Selassie Ethiopian Orthodox Church
Organizer
Roleystone, WA
Kidist Selassie
Beneficiary

Your easy, powerful, and trusted home for help

  • Easy

    Donate quickly and easily

  • Powerful

    Send help right to the people and causes you care about

  • Trusted

    Your donation is protected by the GoFundMe Giving Guarantee